ይህ መዝገበ ቃላት፥ በመምህር ክፍለ ጊዮርጊስ ተጀምሮ ፥ በአለቃ ኪዳነ ወልድ ክፍሌ፥ ተስፋፍቶና ተብራርቶ፥ በአለቃ ደስታ ተክለ ወልድ ታርሞና ተስተካክሎ፥በ1948 ዓም፥ የታተመው፣ "መጽሐፈ ሰዋስው ወግስ፥ ወመዝገበ ቃላት ሐዲስ" የተሰኘው የግእዝ መዝገበ ቃላት፥ ያማርኛ ፍች፥ ሲሆን ምንም አይነት እርማት ሳይደረግለት፥ለዛሬው ትውልድ ለመጠቀም እንዲያመች ሁኖ፥ በድጋሚ የታተመ ነው። ከመጀመሪያው እትም ለየት የሚያደርገው የፊደሉ ተራ በ "አ፣ በ፣ ገ፣ ደ..." የነበረው፤ በሀ፣ ለ፣ ሐ፣ መ... ፐ መሆኑ ብቻ ነው። እነዚህ ከላይ የተጠቀሰው መጠነኛ ለውጥ የተደረገበት ምክንያት፥ በዋናው ቅጅ ላይ የነበረውን ቃላት የመፈለግ ችግር ለማቃለል ሲባል ብቻ መሆኑን በድጋሚ ለማሳሰብ እንወዳለን።
Bitte wählen Sie Ihr Anliegen aus.
Rechnungen
Retourenschein anfordern
Bestellstatus
Storno







